Friday, November 25, 2022

ጃፓንን ስናነሳ



         Two Victories from A single game-The Japanese

                                             

22ኛው የዓለም እግር ኳስ፡ ውድድር በአረቡ አለም በኳታር አስተናጋጅነት እየተከወነ ሲሆን ገና ከማለዳው በርካታ ከግምት የራቁ እውነታዎችን ማስተናገዱን፤ ተያይዞታል፡፡ ከ 32 ቱ የኳሱ አለም ተፋላሚ ሀገራት መካከል አፍሪካ 5 ተወካዮች፡ አሏት፡፡ እስከአሁን ከተስተናዱት አዲስ የመሰሉ ክስተቶች መካከል ጃፓኖች የፈጸሙትና ለአለም በተግባር ያሳዩት ድንቅ ስራ ነው፡፡ በርግጥ ለእኔ ዘመን የፌስ ቡክ መረጃ ቃራሚ ትውልድ ካልሆነ በስተቀር ጃፓኖች ጽዳት የህይወታቸው አንድ አካል እንደሆነ ብዙዎች ይመስክሩላቸዋል፡፡  ተማሪ እያለሁ፡ በተለይም እስከ ስምንተኛ ክፍል ድረስ ሁሌ አርብ አርብ በቡድን እየተመደብን መማሪያ፤ክፍላችንን እናጸዳ ነበር፡ ያም ክፍል ማጽዳት፤ ማጽዳት ከተባለ ማለቴ፤ ነው፡፡ ወለሉን ሞልቶት የነበረውን አቧራና አፈር በቅጠል እየጠረግን በግድግዳ፤ጠረጴዛና ወንበር ብሎም በራሳችን ልብስና ሰውነት ላይ፤ የመቀመጫ ቦታውን እንዲቀየር እናደርጋለን እንጂ እንደማነጻዳው፡ አስታውሳለሁ፡፡ ጃፓን ግን ተማሪ ብቻ ሳይሆን መ/ራን ጭምር ክፍላቸውን እንደሚያጸዱ፡ በአለም ዋንጫው ሰበብ ሰማን፡፡

ጃፓንን ስናነሳ፡ የቶክዮ አሎምፒክ ጀግናችንን አበበ ቢቂላን፡ አንጋፋው የስነጽሑፍ ባለሙያችንን ክብር ዶ.ር ከበደ ሚካኤል ጃፓን እንደምን ሰለጠነች የሚለውን መጽሐፍ፡ ሩቅ ምስራቅ ሳለሁ ጃፓኑዋን ወድጄ በማለት በድምጹ ስለጃፓኑዋ ወጣት ያዜመውን ክቡር ዶ.ር ጥላሁን ገሰሰን፡ እናስታውሳለን፡፡ ጃፓን ተጋጣሚዋን አሸንፋ፡ ደጋፊዎቿ ቡድናቸውን ደግፈው ለጭፈራ አልወጡም፡ ይልቁንም፤ ደስታቸውን በውስጣቸው ይዘው የተቀመጡበትንና ድል ያደረጉበትን ቦታ ጽድት አድርገው፡ ለቀጣዩ ጨዋታ አስተካክለው፡ አለምን አስተምረው፡ ከስታዲዮሙ ወጡ እንጅ፡፡ ይህ በሆነ በሁለተኛው ቀን፡ ከስራ ወደቤቴ ፡ለመግባት ወደ 500 ሜትር ሲቀረኝ፡ የወጣትነት እድሜን በግድ እንለቅም የሚሉ ሶስት ኢትዮጲያዊያን፡ ሲዝናኑ ከቆዩበት ቦታ ከተጎነጩት መጠጥ ጋር በተሰጣቸው አማርዝኛ( አማርኛ እናእንግሊዘኛ) ስለጃፓኖች ጽዳት እያወሩ ሳለ እንድደግፋቸው ይመስላል፡ ደስ በሚል የመጠጥ ፈገግታ ኃሳቤን ጠየቁኝ፡ አንደበቴን ሳላወጣ ድጋፌን እንደነርሱ መለስኩላቸው፡፡ አቦ ይመችሽ ያራዳ ልጅ ብለውኝ የምስጋና ጎርፍ አወረዱልኝ፡፡ ወደ ተመሳሳይ አቅጣጫ ጥቂት እንደተጓዝን አንዱ ወደ ዳር ወጣና የግሉን ቧንቧ ከታችያው የሰውነቱ መንደር አውጥቶ፡ እውነተኛውን ባህሪውን ሲያስተናግድ ጓደኞቹም ሲከተሉት በግርምት ሳያቸው፡ ያራዳ ልጅ የሚለው አንደበት፡ ፈጠን ብሎ ሸባው ምነው፡ አንችም ማስለቀስ፡ አማረሽ እንዴ ብሎ፡አንዱ ሲናገር በሳቅ ፈረሱ፡፡ ሳቃቸውን እንደምን እስከሚጨርሱ ጠብቄ  እኔ እንኳ ቅድሙ ጃፓንን ያደነቃችሁበት ጭውውታችሁ፡ ለምን እናንተስ አልተገበራችሁትም ብዬ ገርሞኝ ነው ስላቸው፡ አባ ከየት ነው ከብልጽግና፤ ከኢዜማ ወይስ ከሊግ ብለው አሁንም በራሳቸው አለም በሳቅ ፈረሱ፡ ከዚያ በሁዋላ መልስ መመላለሱ ተጨማሪ ዳፋ አይጠፋውም ብዬ ወደቤቴ አቀናሁ፡፡ የወጣቶቹ ድርጊት ግን ከውስጤ ቶሎ ሊጠፋ አልቻለም፡ እንዴውም ህዳር 12 ፡ ህዳር ሲታጠንን አስታወሰኝ፡፡

በቀደመው ታሪካችን ህዳር 12 በየኣመቱ ጽዳት ተደርጎ፡ቆሻሻ፤ይቃጠል ነበር፡፡ በዚያ ዘመን በዚያ አስተሳሰብ፤ በዚያ ዘመን በአለ የአለም የአየር ንብረት፡ የሚከወን ስለነበር፡ ስለእርሱ ሂስ ማንሳቱ ጠቃሚ አይመስለኝም፡፡ የጽዳቱ መነሻ ከታች ያለው ነው፡፡

20ኛው ክፍለ ዘመን በመላው ዓለም 1914 እስከ 1918 .. መነሻውን አሜሪካ ያደረገው በተለምዶ ስፓኒሽ ፍሉ የሚባለው ወረርሽኝ በዓለም ላይ 15 ሚሊዮን የሚደርስ ሕዝብ ህይወት እንደቀጠፈ በታሪክ ይነገራል። ይህ ወረርሽኝ በተከሰተ 10 ወራት በኋላ 1911 . በኢትዮጵያ የበርካታ ዜጎችን ህይወት ቀጥፎ አልፏል። በዚህም ምክንያት ይህ ቀን በርካታ ኢትዮጵያውያን የሞቱበት በመሆኑ በቀኑም የፅዳት ዘመቻ እንዲደረግ በአዋጅ ተነግሮ ስለነበረ ከዚህ አዋጅ በኋላ እንደ ባህል ተወስዶ በየዓመቱ ህዳር 12 ሲመጣ በአብዛኛው የሀገራችን አካባቢዎች ነዋሪዎች መንደራቸውን የማፅዳት ሥራ ሲያካሂዱ ቆይተዋል።

አሁን በደረስንበት የአስተሳሰብ ደረጃ፡ የአለም ሙቀት መጠን መጨመር የበካይ ጋዞች ወደ ከባቢ አየር በመግባት እየፈጠሩት ካለው፡ ችግርና በአይናችንን እያየነው ካለነው በርካታ ሁነቶች አንጻር ቆሻሻን ሰብስቦ ማቃጠል፡ አይመጥነንም፡፡ ቆሻሻን፤በቡድን በግል፤ በዘመቻ፡ በሳምንታዊ ወርሃዊና አመታዊ በዓላት፡ማጽዳት እጅግ የሚያስመሰግን ተግባር ነው፡፡ ግን ግን ሰብሰብነው ቆሻሻ የምናስወግድበት መንገድ አስተማሪ፤ እግርና ከማቆሸሽ አልፎ የመተንፈሻ አካል የሚጎዳ ይባሱኑ ከባቢ አየሩም የሚጎዳ መሆን የለበትም፡፡ የአፍሪካዊያኑ መዲና፡ አዲስ አበባ ባለስልጣናት ግን ትጥቃቸውን አሳምረው፡ ህዝባቸውን አስከትለው፡ ለጽዳት መውጣት እንጂ ስለአወጋገዱ ብዙ የሚገዳቸው አይመስልም፡፡ ገራሚው ነገር ደግሞ የሀገሪቱ ብሎ የአዲስ አበባ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ፡ባለስልጣን ጽ/ቤቶች መቀመጫ እዚሁ አዲስ አበባ ሆኖ፡ ችግሩ ፡ ግን መቀጠሉ ነው፡፡( ለችግሩ አለመፈታት የሁላችንም ችግር ቢሆንም መ/ቤቶቹ ግን የተሰጣቸው ተግባርና ኃላፊነት ጭምር ስለሆነ ብዬ ነው፡ ደግሞ እኮ ባለስልጣን ነው) ከታች የተያያዙት ሁለት ሳንሳዊ ጥናቶች በተለይም አንዱ ከህዳር ሲታጠን ጋር ቀረበ ግንኙነት ስላለው፡ ቆሻሻን ማቃጠል ከፍተኛ ጉዳት እንዳለው ያስረዳናል፡፡C:\Users\user\ENAB Dropbox\Wogderes Ejigu\PC\Desktop\Impact of open burning of refuses on air quality.pdf

C:\Users\user\ENAB Dropbox\Wogderes Ejigu\PC\Desktop\Toxic substance from plastic waste.pdf

ማጠቃለያ፤ ቆሻሻን ማጽዳት ልምዳችን ይሆን ፡ ቤታችንን አጽድተን በግቢያችን ግቢያችንን አጽድተን በመንገድ ላይ ቆሻሻን በመድፋት፤ አግባባዊ ባልሆነ መንገድ ቆሻሻን ማስወገድን ግን ልናስቀር;

ይገባል፡፡Description: World Cup: Japa Fans Clean Up Stadium after Historic Win ...


No comments:

Post a Comment

                             ገበር አምባ                    ስራ ፈቶ ሲያሽ ያንች ተመልካች                       በውበት ቁንጅና ማን ነበር እንዳንች፡፡          ...