Wednesday, April 22, 2026

ባህርዳር

 

                          


እስከአሁን ካየሁዋቸው ቦታዎች ሁሉ በልቤ የተለየ ቦታና ፍቅር ያላት ባህርዳር ናት:: ባህርዳር ለሁሉ ነገር የመጀመሪያ ናት:: ያለቤተሰብ ተከታይነት ለብቻዬ አንድ ቀን ተኩል የተጓዝኩባት፤ መኪና ካስተዋወቅን በፍጹም ከዚ ቀን በፊት ከማላውቀው ከአሰላ ከመጣ ልጅ ጋር አብረን በአንድ አልጋ ላይ ያደርኩባት፤ብር በባንክ ተልኮልኝ የተቀበልኩባት፤ በርታ የወደፊት ማንነቴን የሚቀይሩ ውሳኔዎችን በራሴ ወሰንኩባት ቦታ ስለሆነች ባሀርዳር ለእኔ ልዩ ናት:: ጋዜጠኛ ሄኖክ ጎንደር ሴት ብትሆን ደጋግሜ የማገባት እኔነኝ እንዳለው፤ እኔም ባህርዳርንበሴት ጾታ ከመጠራት አልፋ ሴት ብትሆንና ድጋሚ ማግባት ቢፈቀድ የማገባት ይመስለኛል:: ምስጋና ለአይነስውሩ የአማርኛ አስተማሪያችን ጋሽ ክንፈ ይሁንና ፍቅር እስከመቃብር መጽሐፍን 11ኛ ክፍል እያለን አስነብበውን ስለነበር፡ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ስገባ ወደ ባህርዳር ለመሄድ በጣም ጓጉቼ ነበር፡ በመጽሐፍ የተገለጡት ቦታዎችን ለማየት፡ ዲማ ጊዮርጊስን፤የአባይ በረሃን፤ የእናቴ ሞክሼ የሆኑትን ወ/ሮ ውድነሸ በጣሙን፤ፊታውራሪ መሸሻን፡ በዛህንና በልጅነቴ ያየሁዋቸው የነበሩትን የቆሎ ተማሪ መኖሪያ ዳስ(ጎጆ) ቤቶችንና የተማሪዎችን አኮፈዳ

የተማሪ ወዳጅ ይቅር ምናባቱ

ዱላ ሲያነሱበት ይላል ባዛኝቱ::

 እየተባላ የተገጠመላቸውን የቆሎ ተማሪዎች ለማየት:: ተማሪ ሲባል የአስኮላውን ሳይሆን ቆሎ ተማሪን እንደሆነ ይታወቅልኝ::

የባህርዳር ግን የመጀመሪያ ጉዞዬ፤ በጣም አስፈሪ ነበር::የሰላሌ ሜዳዎችን ጨርሰን ድንገት ሳላስበው መኪናችን አባይ በረሃ ውስጥ ጎዞውን ሲጀምር በሁሉም አቅጣጫ አድማስ እንጂ መሬት ማየት ስላልቻልኩ፤ ያ በፊት ሲያወራ ሲያውካካ የነበረ ሁሉ ሰው ፀጥ ሲል ልቤ በፍርሃት ርዶ፤እንባዬ መውረድ ጀመረ:: አብዛኛው አውቶቡስ የሞላው ተማሪ ስለሆነና ሁሉም በሚባል ደረጃ ለቦታው አዲስ በመሆኑ ማንም ማንን አያይም፡ሁሌም በራሱ ስሜት የተያዘ ይመስላል፨ በአባይ በረሃ በየመንገዱ ላይ አደገኛ ናዳ ስላለ ተጠንቀቁ የሚል ጹሑፍ አለ:: ከተወሰኑ አመታት በሁዋላ ያንን ጹሑፍ ሳስታውሰው፤ እንዴው ናዳ ከላይ ቢመጣ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ሊገባኝ አልቻለም፨ የኢትዮጲያ መድህን ድርጅት የለጠፈው አርማ ግን ተስፋ ሰጭ ይመስለኝ ነበር:: ለፍተው ላፈሩት ንብረትዎ ለማትተካ ህይወት መድህን ይሁን አለኝታዎ የሚል ታፔላ::እኔ መድህን ምንእንደሆን በደንብ ባይገባኝም ደስ የሚል ስሜት ፈጥሮልኝ ነበር:: ሞጣ ያደረው አውቶቡሳችን በቀጣይ፤ ቀን ጥዋት ወደ 3 አካባቢ አዴት ከተማ ደርሶ፤ ለትንሽ ደቂቃ ሲያቆም የተጠበሰ በቆሎ ገዛሁ፡ በቆሎ ለመጀመሪያ ጊዜ ቀመስኩ:: የሚያሳዝነው ዕለቱ ረቡዕ ስለነበር ከሁዋላችን የነበሩ አንድ በእድሜ ዘለግ ያሉ አባት አይ የሸዋ ሰው ጾም የለም እንዴ፤ በጠዋት ምግብ ብለው የምንበላውን ሲያበሻቅጡን አንድ ጊዜ ብቻ አፌ ውስጥ ያለውን ውጬ ሌላውን መብላት አቆምኩ:: ከላይ ያለውን አምላኬን ሳልፈራ አጠገቤ ያሉትን ትልቅ አባት ፈርቼ::

አይደርስ የለ ባርዳር በሁለተኛው ቀን ወደ አምስት ሰአት አካባቢ ደረሰን፡ ሁላችንም በአንድነት ወደ ፔዳ ግቢ ገባን:: እንደደረስን የመጀመሪያ ምዝገባ ስለነበር ለመመዝገብ ፎቶ ከፒ ስለሚያስፈልግ ብዙዎቻችን ፎቶ ኮፒ ስላልነበረን ሲኒየር ተማሪዎች ካፌ ፎቶ ኮፒ እንዳለ፤ሲነግሩን ግር ብለን ሄድን፤እዚያ እንደደረስን የሻይቡና ማሽን የሚያሞቅ ልጅ አይተን ፎቶ ኮፒ ፈልገን ነው ስንለው ቁጭ በሉ ማሹን እያሞቀሁ ነው ብለን ቁጭ አልን፨ ከተወሰኑ ደቂቃዎች በሁዋላ ሌሎች ሲኒየሮች መሸወዳችን ገብቷቸው፤ይህ የሻይ ማሽን እንጂ የፎቶ ኮፒ ማሽን አይደለም ብለው ፡ ነገሩን:: ሽወዳ ቁጥር አንድ፨

ምዝገባው በዚሁ መልኩ አለቀና ሚሊካርድ ባይኖረንም ካ ገብተን ምሳ በላ:: ምሳ ለመብላትም ሰልፍ መኖሩን አወቅን::ከምሳ ሁሉም ተማሪ ፎቶ ኮፒ አለ ወደተባል ነው ቤት ያመራል፡ወደ ሻይ ቤት ማለት ነው፨ ስንደርስ የተወሰኑ ተማሪዎች ሰልፍ የመሰለ ነገር ሰርተው ግርግዳውን ይዘው ያወራሉ፤ ሲኒየሮች ናቸው፤ ተሰለፉ አሉን፤ ተሰለፍን፤ የተወሰነ ፍሬሽ እየመጣ እኛን ተከትሎ ይሰለፋል:: ሌሎች ግን ዝም ብለው ይገባሉ፤ አሁን እኛ ፍሬሽ ስለሆንን አውቀው ነው ሰልፍ ሳይጠብቁ የሚገቡት እያልን ውስጣችን ሲያማቸው፡ ከፊታችን ተሰልፈው የነበሩት ልጆች እየሳቁ ትተውን ሄዱ:: ሽወዳ ቁጥር 2:: ከዚያ ገባን ስንገባ በግራ በኩል ትንሽ ክፍል ውስጥ አለ፨ ቲኬት ከዚያ ይገዛና ሻይ ራስህ ሄደህን ነው የምትወስደው:: እኛ ገብተን ቁጭ አልን፡ የሚያመጡልን መስለን፡ ቁጭ እንዳልን አንዱ መጣና ፍላጎታችንን ጠየቀን ተናገር፡ የታዘዘን ልጅ ወዴት እንደሄደ አላወቅንም:: የሻይ ቤቱ ሰራተኛ ብርጭቆ ሲሰበስብ፡ እኛ እኮ አዘናል ፤አልደረሰንም ሲለን ቁጭ በሉ ይመጣላችሁዋል ብሎን ቁጭ አልን::ከተወሰኑ ደቂቃዎች በሁዋላ እንደተሸወድን ገባንና ተነስተን ወጣን::

በዚህ በዚህ መልኩ እየተሸወድን ከተወሰኑ ቀናት በሁዋላ፤ዲፖርትመንት መረጥን ኦረንቴሽን ሳይሰጠን ቤተመጻህፍት ቤት መግባትም ጀመርን:: አንድ እኔ የማውቀው ትንሽ ግንዛቤ ያለው የሚመስል ጓደኛችን እንግባ ብሎኝ ገባን:: የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ በነበርኩበት ወቅት የቤመጻህፍት ክበብ አባል ሆኜ ተማሪ አስተናግድ፤የምፈልገውን መጽሐፍ ቀድሜ አውጥቼ ተማሪ ወስዶታል እያልኩ አነብ ስለነበር ትንሽ ግንዛቤው ቢኖረኝም ይህ፤ጓደኛዬ ግን  ትንሽ ደፋር ፈጣን ነገር ስለሆነ ካታሎግ ሲያገላብጥ አንድ የመጽሐፍ ርዕስ አገኘና ፤ገንጥሎ ሰርኩሌሽን ዴስክ ሄዶ ስጡኝ ሲላቸው፤ የቤተመጻህፍቱ ሰራተኞች ተጠራሩና አጭር ስብሰባ አድርገው መታወቂ አም አሉት አዲስ ነኝ የለኝም አላቸው፡ ወዲያውኑ፤ አንድ ሰራተኛ አጭበጨበና ፍሬሽ ተማሪዎች ውጭ ስለምትፈለጉ ውጡ ሲን ገብተን የነበርነው ሁሉ ወጣን፡ ወዲያውኑ ፍሬሽ ተማሪዎች ኦረንቴሽን ሳይሰጥ ወደ ቤተመጻህፍት ቤት ዝር እንዳትሉ የሚል ማስታወቂያ ተለጠፍ:: ከተቀመጡት ምክንያቶችየመጀመሪያው ካቶግ መቅደድ የሚል ጓደኛዬ ገበና ነው::

 

No comments:

Post a Comment

                             ገበር አምባ                    ስራ ፈቶ ሲያሽ ያንች ተመልካች                       በውበት ቁንጅና ማን ነበር እንዳንች፡፡          ...