Friday, November 11, 2022

ተው ዘገየህ

ዛሬ ህዳር 1/2015 . ወደ ስራ ሳመራ የተሳፈርኩበት ተሸከርካሪ፡ ውስጥ ከአንድ ሬዲዮ ጣቢያ የተለቀቀ ቆየት ያለ ዘፈን በድንገት ማሰማት ሲጀምር ሶስት አስርት አመታትን ወደ ሁዋላ ይዞኝ በትዝታ ሸመጠጠና ሳላስበው ሳቅሁ አንዲት እናት ምነው ልጄ ምንአይተህነው የምትስቀው ብለው እስኪያናግሩኝ ድረስና ከትዝታ ባህር ሳልሰጥም ሲያወጡኝ ነበር ውስጤ የተናጠው፡፡ ባለቤቴ ይህንን ዘፈን አልሰማችሁ ካልሆነ በስተቀር ትደውልልኝ ነበር፡ታሪኩን ስለምታውቀው፡፡

ከሠላሳ አመት በፊት አንድ ጥፋት አጠፋሁና ብዙም፡ማገናዘብ፤ ባልቻልኩበት የለጋ ዕድሜ አንድ ከናድ ውሳኔ ወሰንኩ፡፡  የጥፋቱን ክብደት፡ በዚያ ዘመን የማገናዘብ ችሎታዬ ሳስበው፡ከባድ ስለነበር ራሴን፡ ካደግሁበት ቦታ መሰወር ወይም መሞት ነበር፡ውሳኔ፡፡ ተወልጄ ካደኩሁበት ቦታ  ወደሌላ ቦታ መጥፋትና ራስን መሰወር ወይንም በኪሴ የነበረችው አስራ ሰባት ብር እካለቀች ድረስ በህይወት መቆየት ከዚያ በሁዋላ የክብር ሞት መሞትን መረጥሁ፡፡ ለዚያች ጥፋት ሞትን መምረጤ ምን ያክል የገዘፈ ጥፋት እንደሆነ የገባኝ አንዲት: የቅርቤ የምላት ነርስ ጓደኛዬ የአንድ ህመምተኛዋን ታሪክ ባወጋችኝ ጊዜ ነው፡፡ ጓደኛዬ እንደነገረች፡ህምተኛዋ ራሱን ለማጥፋት መርዝ ጠጥቶ ለመሞት እያጣጣረ ሳለ፡ የአካባቢው ሰው፡ የወሳንሳ ይዘው  እርስዋ ወደምትሰራበት ጤና ጣቢያ ወስደውት የመጀመሪያ ርዳታ፡ እንዲያገኝ፡ በሚደረግ፤ ግብግብ ውስጥ ወተት ፈልጉ ብላ  ወተት ተፈልጎ መጥቶ እንዲጠጣ  ሲቀርብለት ፡ አስገራሚውም ግለሰብ፡ዛሬ ረቡዕ ነው እኔ እጾማሁ አልጠጣም ያለውን የታማሚዋን ታሪክ ነግራኝ፡ አምላክ የሰራውን ቤተመቅደስ ሰውነቱን ለማፍረስ ህግ አልፈራ፡ ጾም መሻር እንቢ አለ ቤተክርስቲያን ያላት ትውልድ ይህ ነው ስትለኝ፡ በታማሚዋ በኩል አርጩሜው ለኔም ነበር የደረሰኝ፡፡

ወደ ቀደመው ትዝታዬ ልመለስና፡ራሴን ችዬ ከወላጆቼ ቤት እስከወጣሁበት ድረስ ያለወላጆቼ፤ እውቅናና ፈቃድ ውጭ ያደርኩት በእነዚያ 3 ቀናት ብቻ ነበር፡፡ የጠፋሁበት ጉዳይ ያስጠፋ ነበር ወይስ አያስጠፋም የሚለው ብዙ አነጋጋሪ ቢሆንም ለእኔ ግን በዚያን ወቅት ትልቅ ጥፋት ነበር፡፡ እኔ ጠፍቼ ወላጆቼና ዘመዶቼ በወርሃ ነሀሴ 3 ቀናት የለፉትን ልፋትና እንግልት ሳስበው ውስጤ ያዝናል፡፡እድሜ፡አቻዬ ከእናቴ ጋር ውሃ ወስዶት ነው እያሉ ወንዝ ውስጥ ሲፈልጉ ወራጅ ውሃ ሊወስደው በመከራ ነበር የተረፈው፡ አብሮኝ ይማር የነበረና ትምህርቱን አቋርጦ የነበረ ሌላ ጓደኛዬን አንተ የት እንደሄደ ታውቃለህ አምጣ እያሉ ያስጨነቁት፤ ሌላም ሌላም ነገር ሳስበው ግርም ይለኛል፡፡ በጣም የሚገርመው ይህ ሁሉ ሰው፡ እኔን ለመጥፈት ያነሳሳኝ፡ ጥፋቱን ቢያውቅ ምን ያክል እንደሚስቅብኝ ነው፡፡

እና በዚያ በወርሃ ነሐሴ 1314 እና 15 አንድ ከተማ ላይ ቁጭ ብዬ ውሎየን የማሳልፈው ሙዚቃ ቤቶች አቅራቢያ ነበር፡፡ ይህ ዛሬ የሰማሁት ዘፈን አዲስ የወጣና 2 አንጋፋ ወንዶችና 2 አንጋፋ ሴቶች፡ በቅንጅት ያወጡት ነበር፡፡ በሙዚቃው መካከል ስለሙዚቃው የሚነገር ማስታወቂያ ሙዚቃውን ተከትለው አብረው የሚዘፍኑየሚጨፍሩና የሚደንሱ ታዳጊዎች፤ከመንገዳቸው እርምጃቸው ቀንሰው ሙዚቃውን የሚሰሙ ሰዎች መንገዶኞች፤ ጫማዎቻቸውን፡ የሚያስጠርጉ፡ ሰዎች፤ ከአዲስ አበባ ተነስተው ወደ ሰሜን ኢትዮጲያ የሚጓዙ ሀገር አቋራጭ አውቶቡሶች፡ጋሪዎች ሁሉም፡ ነገር አሁንም ፍንትው ብሎ ይታየኛል፡፡ እናም ዛሬ ያንን ዘፈን ስሰማ፡ ያሁሉ ትዝታዬ ነበር ፊቴ የተደቀነው፡፡ በወላጆቼ ብርታትና በአምላክ ፈቃድ እራሴን አጣፈለሁ ያልኩት ልጅም ራሴን ሳላጠፋ መሀል መንገድ ላይ አባቴ አገኘኝ፡፡ አባቴ ከርቀት አይቶኝ ስሜን ሲጠራ፡ እንባዬን ለቀቅሁት፡ የአባቴ እንባ ዛሬም ይታየኛል፡፡ ልክ ከሞት የተነሳሁ ያክል ነበር፡ ፊቱ የደስታ ጸዳል ሞልቶታል ግን ያለቅሳል፡፡ አባቴ እኔ ላልቅስልህ በጥፋቴ፡ አስለቀስኩህ፡፡ እና ያወደ ሁላ በትዝታ ያስኬደኝ ዘፈን መሀሙድ አህመድና ብዙነሽ በቀለ 

ተው ዘገየህ አንተ ዘው ዘገየህ ቆሜ

መራመዴን መሄዴን እያየህ፡፡ በመባባል በቅብብል፡

የሚዜሙት ዜማ ነበር፡፡

ትዝታ መልካም ነው፡ ያንን ሁሉ ጊዜ አስታወሰኝ፡፡


No comments:

Post a Comment

                             ገበር አምባ                    ስራ ፈቶ ሲያሽ ያንች ተመልካች                       በውበት ቁንጅና ማን ነበር እንዳንች፡፡          ...